Up next


ሰበር ዜና ፡ በመፈንቅለ መንግስቱ ሰዓት ከአሳምነዉ ጋር አብሮ የነበረው ባለስልጣን ሙሉ መረጃውን አወጣ

155 Views
zehabesha
2
Published on 02 Jul 2019 / In News & Politics

ሰበር ዜና❗️

#Ethiopia : ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓም አቶ Asemahagn Aseres የአማራ ክልል የመንግሥት ኮምዩንኬሽን ቢሮ ኃላፊ በብር ሸለቆ ሰልጥነው በተመረቁ የልዩ ኃይል አባላት የክልሉ አመራሮች በሚኖሩበት ባለ ሁለት ፎቅ የእንግዶች ማረፊያ ታግተው እንደነበር ለ Amhara Mass Media Agency ተናግሩ። ብርጋዴር ጄኔራል አሳምነው ጽጌ ሰማያዊ ሸሚዝ ለብሰው በእንግዳ ማረፊያው ነበሩ። በወቅቱ ከእንግዳ ማረፊያው ውስጥ ወደ #FSR አይሱዙ እቃ እየተጫነ ነበር። ( ምን እንደሆነ አላወቁም፣ መሳሪያ፣ ጥይት ሊሆን እንደሚችል ይጠረጥራሉ) ብርጋዴር ጄኔራል አሳምነው የነበሩበት እንግዳ ማረፊያ ከፍተኛ ጥበቃ ይደረግለት ነበር። አሳምነው "በለው" እያሉ ትዕዛዝ ይሰጡ ነበር። ቦምብ እና የከባድ መሳሪያ ተኩስ መስማታቸውን ተናግረዋል።

Show more
Facebook Comments

Up next